1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አሸናፊ ያልተለየበት የፈረንሳዩ የምክር ቤት ምርጫ እና አንድምታዉ

ሰኞ፣ ሐምሌ 1 2016

ፕሬዚዳንት ማክሮ ካቢኔያቸዉን በትነዉ ለዳግም ለሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ፤ መጥራታቸዉን ተከትሎ በተካሄደዉ ሁለተኛ ዙር ምርጫ አብላጫ ወንበሮችን ያገኙ እና መንግሥት ለመመስረት በቂ ዉጤት ያላገኙ ፓርቲዎች በጥምረት ለመስራት ለድርድር እና ለስልጣን ክፍፍል ተስማምተዉ መቀመጥ እንዳለባቸዉ ተመልክቷል። የምርጫዉ ዉጤት ያልተጠበቀ ተብሏል።

አሸናፊ ያለየበት የፈረንሳዩ የምክር ቤት ምርጫ 2024
አሸናፊ ያለየበት የፈረንሳዩ የምክር ቤት ምርጫ 2024ምስል Lionel Urman/ABACAPRESS/IMAGO

አሸናፊ ያለየበት የፈረንሳዩ የምክር ቤት ምርጫ

This browser does not support the audio element.

አሸናፊ ያለየበት የፈረንሳዩ የምክር ቤት ምርጫ

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኤማኑኤል ማክሮ ከሦስት ሳምንት በፊት በተካሄደዉ በአውሮጳ ህብረት የምክር ቤት ምርጫ ፓርቲያቸዉ ከባድ ሽንፈት ከገጠመዉ ወዲህ ካቢኔያቸዉን በትነዉ ለዳግም የምክር ቤት ምርጫ፤ መጥራታቸዉ ይታወቃል። በፈረንሳይ ባለፈዉ ሳምንት እሁድ የተካሄደዉን የመጀመርያ ዙር ምርጫ ተከትሎ ትናንት እሁድ በተካሄደዉ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ፤ ዉጤት አስደናቂ እና ያልተጠበቀ ተብሎለታል። ይፋ በተደረገዉ ዉጤት መሰረት፤ ፖፑላር ፍሮንት (NPF) የተሰኘዉ የግራ ዘመም ፓርቲዎች ጥምረት በአስደናቂ ሁኔታ አብላጫውን ድምፅ ማግኘቱ ተመልክቷል። በዚህም የግራ ዘመም ፓርቲዎች ጥምረት በምክር ቤት 171 ወንበሮችን ፤ የፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮ  ማዕከላዊ ፓርቲ 152 ወንበሮችን እንዲሁም  በመጀመርያ ዙር አብላጫ ድምፅን አግኝቶ የነበረዉ፤ ስደተኛ ጠል የሚባለዉየማሪን ለፐን ፓርቲ ናሽናል ራሊ ፓርቲ ደግሞ 134 ወንበሮችን በማግኘት ሦስተኛ ደረጃን መያዙ ታዉቋል።  ይሁንና ሁሉም ፓርቲዎች መንግሥትን ለመመስረት በቂ መቀመጫን አላገኙም። በምርጫዉ ዉጤት መሰረት አብላጫ ወንበሮችን ያገኙ እና መንግሥት ለመመስረት በቂ ዉጤት ያላገኙት እነዚህ ፓርቲዎች በጥምረት ለመስራት ለድርድር እና ለስልጣን ክፍፍል ለመቀመጥ መስማማት እንዳለባቸዉ ተመልክቷል። የፈረንሳዩን የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የሁለተኛ ዙር ምርጫ ዉጤትን በተመለከተ ፈረንሳይ ፓሪስ የምትገኘዉን ወኪላችን አነጋጋረናታል።

 

ሃይማኖት ጥሩነህ

አዜብ ታደሰ

ፀሃይ ጫኔ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW