አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በለንደን አቀባበል ተደረገላቸው
ሰኞ፣ ሰኔ 11 2010ማስታወቂያ
በቅርቡ ከእስር የተፈቱት የግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነት እና የዴሞክራሲ ንቅናቄ መሥራቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በሚኖሩበት ብሪታኒያ ትናንት ማምሻውን አቀባበል ተደረገላቸው። አቶ አንዳርጋቸውን ለመቀበል በለንደን ከተማ በተዘጋጀው መርኃ-ግብር ላይ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ ኣውጪ ግንባር (ኦብነግ) የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አብዱረሕማን መሐዲን ጨምሮ የተቃውሞ ፖለቲከኞች፣ ደጋፊዎቻቸው እና በብሪታኒያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ታድመውበታል። አቶ አንዳርጋቸው በወቅቱ ባሰሙት ንግግር እንዲፈቱ ለወተወቱ ሁሉ ምሥጋቸውን አቅርበዋል።
አቶ አንዳርጋቸው ከእስር ከተፈቱ በኋላ አዲስ አበባ ላይ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸው ነበር። በልዩ ሁኔታ ይቅርታ ተደርጎላቸው ከእስር የተፈቱት አቶ አንዳርጋቸው ወደ ብሪታኒያ ከመጓዛቸው በፊት ጠቅላይ ምኒስትር አብይ አሕመድን አግኘው ማነጋገራቸው አይዘነጋም። በለንደን ከተማ ትናንት ማምሻውን የተዘጋጀውን የአቀባበል መርኃ-ግብር የተከታተለችው ሐና ደምሴ የሚከተለውን ዘገባ ልካልናለች።
ሐና ደምሴ
እሸቴ በቀለ