1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አቶ ጃዋርን ጨምሮ በሽብርተኝነት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ዉሎ 

ሰኞ፣ መስከረም 11 2013

አቶ ጃዋር መሃመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሃምዛ አዳነ እና ሌሎችም በክስ መዝገቡ የተያዙት 18 ሰዎች ዛሬ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበዋል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አቶ ጃዋርን ጨምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙና ከሃገር ውጭ በሚገኙ 24 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብርተኝነትና ሎሎች በርካታ ክስ መስርቻለሁ ማለቱ ይታወቃል፡

Symbolbild Gericht Gesetz Waage und Hammer
ምስል Fotolia/Sebastian Duda

ፖሊስ ለቀጣይ ሃሙስ ቀርቦ መልስ እንዲሰጥ ቀጠሮ ተሰጥቶአል

This browser does not support the audio element.


እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ለፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ አቶ ጃዋር መሃመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሃምዛ አዳነ እና ሌሎችም በክስ መዝገቡ የተያዙት 18 ሰዎች ዛሬ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበዋል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ባለፈው እለተ ቅዳሜ አቶ ጃዋርን ጨምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙና ከሃገር ውጭ በሚገኙ 24 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብርተኝነትና ሎሎች በርካታ ክስ መስርቻለሁ ማለቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ላይ የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ለእለቱ ችሎት በሰጡት ቃላቸው ወንጀሉን እንዳልፈጸሙ በመግለፅ የታሰሩትም በፖለቲከዊ ምክኒያት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች እንደሚሉት በመንግስት ቁጥጥር ስር ለሚገኙ ተከሳሾች ስለተከፈተባቸው ክስ ምንነት ዛሬ ጠዋት ለፍርድ ቤት እስከቀረቡበት ጊዜ ድረስ በእጃቸው የደረሰ የክሱ ዝርዝር ጉዳይ አልተገለጸም፡፡ ዐቃቤ ህግ ክስ ከመመስረቱ አስቀድሞ የክሱን ዝርዝር ጭምር ለተጠርጣሪዎች ማድረስ ነበረበት የሚሉት ጠበቃ ቱሊ ባይሳ ቻርቹ ጠበቆችንም ሆነ ተጠርጣሪዎችን የደረሰው ገና ዛሬ ችሎት ላይ ነው ብለዋል፡፡
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የህግ መመህር የሆኑት ደጀን የማነህ በበኩላቸው ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቅዳሜ እለት የክስ ምስረታውን በሰበር ዜናነት የመውጣቱን ሂደት ተችተውታል፡፡ የክስ ምስረታው የአቃቤ ህጉ የዕለት ተዕለት ስራ ነው ያሉት መመህር ደጀን ከዚያም አስቀድሞ የክስ ቻርጁ በተጠርጣሪዎች እጅ ላይ ደርሶ በጉዳዩ ላይ ከጠበቆቻቸው ጋር የመወያየት መብት ነበራቸው ነው የሚሉት፡፡ ከሃገር ውስጥ ያልቀረቡ 2 ተጠርጣሪዎች በአካል እንዲቀርቡና በውጭ ሃገር የሚገኙ ተጠርጣሪዎችን በተመለከተ ደግሞ ፖሊስ ለቀጣይ ሃሙስ ለተያዘው ቀጠሮ ቀርቦ መልስ እንዲሰጥ ፍርድ ቤቱ በማዘዝ ነው የዛሬ የችሎት ውሎ የተጠናቀቀው፡፡

ስዩም ጌቱ 


አዜብ ታደሰ 
እሸቴ በቀለ 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW