የአፍሪቃ ፓስፖርት
ሰኞ፣ የካቲት 20 2009![Ruanda Idriss Deby und Paul Kagame stellen neuen Reisepass vor](https://static.dw.com/image/19408417_800.webp)
ማስታወቂያ
የአፍሪቃ ህብረት የሰላም እና የፀጥታ ምክር ቤት በክፍለ ዓለሙ የሰዎች እና የሸቀጦች ነጻ ዝውውር ተግባራዊ እንዲሆን አስፈላጊዎቹ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠየቀ ። ባለፈው ሳምንት በዚሁ ጉዳይ ላይ የተነጋገረው ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ ነፃ የሰዎች እና የሸቀጦች ዝውውር የአፍሪቃን ውህደት ያመቻቻል ያፋጥናልም ሲል አስታውቋል ። አፍሪቃውያንን በአባል ሀገራት ውስጥ በነፃ መዘዋወር ያስችላል ስለተባለው ነጻ ፓስፖርት ጉዳዩ ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የኤኮኖሚ እና የፖለቲካ ጉዳዮች አጥኚ እና ተንታኝ ከነጻ ዝውውሩ በፊት በአባል አገራት መካከል የንግድ ትስስሩን እና ኤኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን ማጠናከሩ መቅደም ይኖርበታል ብለዋል ።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ