አናሌና ቤርቦክ የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆኑ
ሰኞ፣ ግንቦት 25 2017
ማስታወቂያ
የቀድሞዋ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ቤርቦክ በኒውዮርክ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ሆነዉ ዛሬ ተሾሙ። ቤርቦክ በዚህ ቦታ ላይ ለመወዳደር የቀረቡ ብቸኛዋ እጩ መሆናቸው ታዉቋል። ከሁለት ሳምንት በፊት ቤርቦክ ቦታዉን ለመዉሰድ ባደረጉት የማመልከቻ ንግግር፣ «በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ ስቴትስ እና በሌሎች ሀገራት ከሚታየዉ የማግለል ዝንባሌ አንፃር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከምንጊዜውም በላይ አስፈላጊ ነዉ» ሲሉ ተናግረዋል።
የቀድሞዋ የጀርመን የዉጭ ጉዳይ ሚኒ ስትር አናሌና ቤርቦክ የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚደንትነት በምዕራብ አውሮጳ አገሮች እና በሌሎች የዓለም ሃገራት ይደገፋል። አዲሷ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዝዳንት አናሌና ቤርቦክ የስልጣን ዘመናቸው የሚጀምረው ከፊታችን መስከረም ወር ይሆናል። ስልጣኑም ለቀጣይ አንድ ዓመት የሚዘልቅ ነዉ።