1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አንድ ለአንድ፤ ከአቶ ልደቱ አያሌው ጋር

ሸዋዬ ለገሠ Shewaye Legesse
ዓርብ፣ ጥቅምት 7 2018

ከ30 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ጉልህ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዛሬም አልታከቱም። እሳቸው ኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ለማምጣት የተሻለ መንገድ ነው ያሉትን የትግል ስልት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለማስረዳት ይጥራሉ። መርኀቸው በሌሎች በርካታ ሃገራት ውጤት አስገኝቷል የሚሉት ሰላማዊ ትግል ነው።

ታዋቂው ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው
ከ30 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የሚገኙት ታዋቂው ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው። ፎቶ ከማኅደርምስል፦ privat

አንድ ለአንድ ከአቶ ልደቱ አያሌው ጋር

This browser does not support the audio element.

 

ከ30 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ጉልህ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዛሬም አልታከቱም። እሳቸው ኢትዮጵያውስጥ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ለማምጣት የተሻለ መንገድ ነው ያሉትን የትግል ስልት ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለማስረዳት ይጥራሉ። መርኀቸው በሌሎች በርካታ ሃገራት ውጤት አስገኝቷል የሚሉት ሰላማዊ ትግል ነው። ፖለቲካዊ እሳቤያቸውን በመጽሐፍ ሳይቀር አሳትመው ለአንባቢያን አቅርበዋል። በተለያዩ ጊዜያት ደጋግመው ታስረዋል፤ አሁን ደግሞ ለስደት ተዳርገዋል።

በ1960ዎቹ መጀመሪያ የተወለዱት አቶ ልደቱ አያሌው በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ከወጣትነታቸው አንስተው ለዓመታት የዘለቁ ታዋቂ ፖለቲከኛ ናቸው። አቶ ልደቱ ከሦስት አስርት ዓመታት በዘለለው የፖለቲካ ተሳትፏቸውም በተለያዩ ፓርቲዎች ውስጥ ከአባልነት እስከ መሪነትና መስራችነት የዘለቀ ተሳትፎ እንደነበራቸው መረጃዎች ያመለክታሉ። በተለይም በ1997 ግንቦት ወር ከተካሄደው ምርጫ ቅስቀሳ ጋ በተገናኘ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች እንደአነቃቂ መንፈስ የተወሰዱበት አጋጣሚም በብዙዎች ይታወሳል።አቶ ልደቱ በዚያው ልክ አወዛጋቢ ሆነው የታዩባቸው አጋጣሚዎች ቢኖሩም እሳቸው ተገቢና ትክክል ነው ያሉትን የፖለቲካ አስተሳሰብ በአደባባይ ከመግለጽ ወደ ኋላ ባለማለትም ዛሬም ቀጥለዋል። በመገናኛብዙሃን ቀርበው ሃሳባቸውን ለማጋራት ወደ ኋላ አይሉም፤ ሞጋችና አከራካሪ ጉዳዮችን ይጽፋሉ፤ አልፈው ተርፈውም መጽሐፍትን ለንባብ አብቅተዋል። የአንድ ለአንድ እንግዳችን ናቸው፤ ሙሉውን ቃለመጠይቅ ለማድመጥ የምድጽ ማዕቀፉን ይጫኑ

ሸዋዬ ለገሠ

ታምራት ዲንሳ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW