አንድ ለአንድ፤ የኅዳሴ ግድብና የዐባይ ተፋሰስ ትሩፋትና ፈተና
ዓርብ፣ መስከረም 9 2018
ማስታወቂያ
መቅደላዊት መሳይ ደርቤ ከውኃ፣ ከከርሰ ምድር ጥናት፣ ከአካባቢ ጥናት ጋር በተያያዘ ሰፊ ጥናትና ምርምርን ያደረጉ የዘርፉ ባለሞያ ናቸው። የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በሲቪል ምህንድስና፣ ሦስት የማስተርስ ዲግሪዎችን ደግሞ በውኃ ኃይል ምህንድስና፣ በአካባቢ ሳይንስና በአካባቢ ጥናት ከአዲስ አበባ፣ ከኔዘርላንድስ እና ከአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች አግኝተዋል። አሁን ደግሞ በፍሎሪዳ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ የከርሰምድር ሥርዓተ ውቅር የፒ ኤች ዲ ጥናታቸውን አጠናቀዋል።
ጥናትና ምርምሮቻቸው በውኃ እና በተፋሰሶች ፍትሃዊ፣ ተመጣጣኝ እና ዘላቂ አጠቃቀም ላይ ያተኮሩ ናቸው። በአባይና በናይል ተፋሰስ ሃገራት ዙሪያም ሰፊ ምርምር እና የጥናት ወረቀቶችን አቅርበዋል። የአንድ ለአንድ እንግዳችን ሆነው በዐባይና በኅዳሴ ግድብ ተጽዕኖ፣ ትሩፋትና ፈተና፤ ከዛም አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባለው አካባቢ ፖለቲካዊ ፋይዳ ላይ ከዋሽንግተን ዲሲ ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀ ጋር ተወያይተዋል።
አበበ ፈለቀ
ሸዋዬ ለገሠ
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር