አዉሮጳና ጀርመን
ማክሰኞ፣ ኅዳር 24 2006ማስታወቂያ
ባለፈዉ መስከረም ጀርመን ዉስጥ በተደረገዉ ምርጫ የመጀመሪያዉን እና ሁለተኛዉን ደረጃ ያገኙት የሐገሪቱ ትላልቅ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተጠማሪ መንግሥት ለመመሥረት ባለፈዉ ሳምንት ተስማምተዋል።በሥልጣን ላይ ያሉት የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ሕብረት/ የክርቲያን ሶሻል ሕብረት (CDU/CSU) መሪዎች ከዋነኛዉ ተቃዋሚ ከሶሻል ዲሞክራቶቹ ፓርቲ (SPD) አቻዎቻቸዉ ጋር ያደረጉት ሥምምነት የሚፀናዉ የSPD አባላት ሲቀበሉት ነዉ።የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ሐይለ ሚካኤል በዛሬዉ አዉሮጳና ጀርመን ዝግጅታችን እንደሚነግረን ስምምነቱ ፀደቀም አልፀደቀ የጀርመን ፖለቲከኞች ከስምምነት እስኪደርሱ ድረስ ያደረጉት ድርድር መቻቻልንና ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገዛትን ያመለከተ ነበር።
ይልማ ሐይለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ