አዉሮጳና ጀርመን
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 30 2001ማስታወቂያ
የተወለዱት ሞሮኮ ነዉ።የኢማም ልጅ ናቸዉ።ሙስሊም በአስራ-አራት አመታቸዉ ወደ ኔዘላንድስ ተሰደዱ።እዚያ ተማሩ።ተቀጠሩ። አሁን ደግሞ የትልቂቱ የወደብ ከተማ ሮተርዳም ከንቲባ ሆኑ።አቡጧሊብ።የአቡጧሊብ በኔዘርላንድስ የመጀመሪያዉ ሙስሊም ከንቲባ መሆናቸዉ ብዙ ድጋፍ እንዳገኘ ሁሉ ተቃዉሞ ገጥሞታል።የመጀመሪያዉ የዝግጅትን ክፍል የአቡጧሊቡን ምርጫና እንድምታዉን ይቃኛል።ሁለተኛዉ የዝግጅታችን ክፍል ደግሞ የአወቅቱን የአዉሮጳ ሕብረትን የፕሬዝዳትነት ሥልጣን የያዘችዉን የቼክ ሪፐብሊክንና የገጠማትን ፈተና ይመለከታል።