1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አዉሮጳ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉን፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ «ይፈፀማል» ያሉትን ግድያ በሠልፍ አወገዙ

ነጋሽ መሐመድ
ረቡዕ፣ ኅዳር 17 2018

በኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በጠራዉ ሰልፍ ላይ የታደሙት ሠልፈኞች እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በተለያዩ አካባባቢዎች «በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ» የሚፈፀመዉን ግድያና ግፍ እስካሁን ማስቆም አልቻለም

ሠልፈኞቹ እንደሚሉት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚፈፀመዉን ግድያ፣ ግፍና ማፈናቀልን ለማስቆም የኢትዮጵያ መንግሥት የወሰደዉ እርምጃ እስካሁን የለም።
በርሊን-ጀርመን አደባባይ ከተሰለፉ ሰልፈኞች በከፊል።ሠልፈኞቹ ኢትዮጵያ ዉስጥ በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ «ይፈፀማል» ያሉት ግድያ፣ እገታና መፈናቀል እንዲቆም ጠይቀዋል።ምስል፦ Tirsit Trimborn

አዉሮጳ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉን፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ «ይፈፀማል» ያሉትን ግድያ በሠልፍ አወገዙ

This browser does not support the audio element.

ጀርመን ዉስጥና በአጎራባች የአዉሮጳ ሐገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለይ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ላይ «ይፈፀማል» ያሉትን ግድያ፣ ግፍና ማፈናቀልን ዛሬ በርሊን-ጀርመን ዉስጥ ባደረጉት የአደባባይ ሠልፍ አወገዙ። በኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጀርመን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት በጠራዉ ሰልፍ ላይ የታደሙት ሠልፈኞች እንደሚሉትየኢትዮጵያ መንግሥትበተለያዩ አካባባቢዎች «በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ» የሚፈፀመዉን ግድያና ግፍ እስካሁን ማስቆም አልቻለም።ግድያ፣ ግፍ፣ በደሉ እንዲቆም ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ጫና እንዲያሳርፍ ጠይቀዋልም። ነጋሽ መሐመድ ከሰልፉ አስተባባሪዎች ፣ ሊቀካሕናት ዶክተር መርዓዊ ተበጀ በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን መስራችንና መላከ መዊ ልሳነ ወርቅ ዉቤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን የጀርመን ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መላከ መዊ ልሳነ ወርቅ ዉቤን በሥልክ አነጋግሯቸዋል። 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW