አዲሱ ትልቁ የጀርመን ጥምር መንግሥት7 ታኅሣሥ 2006ሰኞ፣ ታኅሣሥ 7 2006በጀርመን ምክር ቤታዊ ምርጫ ከተካሄደ ከሶስት ወራት በኋላ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ህብረት፣ በምሕፃሩ ሲ ዲ ዩ እና የክርስቲያን ሶሻል ህብረት፣ በምሕፃሩ ሲ ኤስ ዩ፣ እንዲሁም፣ የሶሻል ዲሞክራት ፓርቲ፣ በምሕፃሩ ኤስ ፒ ዲ አንድ ትልቅ ጥምር መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችላቸውን ሰነድ ዛሬ ተፈራረሙ።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግምስል Reutersማስታወቂያ በጀርመን ታሪክ ውስጥ አንድ ትልቅ ጥምር መንግሥት ሲመሠረት ያሁኑ ሦስትኛው ሲሆን፣ አንጌላ ሜርክል ነገ በጀርመን ፌዴራዊ ምክር ቤት፣ ቡንድስታግ ውስጥ እንደገና መራሒተ መንግ/ስት ሆነው ይመረጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። ሕዝቡ ከአዲሱ ትልቅ ጥምር መንግ/ሥት ምን ይጠብቃል? ይልማ ኃይለ ሚካኤል አርያም ተክሌ ሸዋዬ ለገሠ