1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አፍሪቃ ከፖሊዮ «ነፃ» ወጣች

ረቡዕ፣ ነሐሴ 20 2012

የልጅነት ልምሻ አፍሪቃ ዉስጥ ለመጨረሻ ጊዜ የታየዉ የዛሬ አራት ዓመት ግድም ናጄሪያ ዉስጥ ነበር።ከዚያ በኋላ በተከታታይ በተሰጠዉ ክትባት በየዓመቱ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ለአካለ ጎዶሎነት ከሚዳርገዉ በሽታ አፍሪቃ ነፃ መሆንዋ ተረጋግጧል

Äthiopien | SNNPR started Impfkampaqne gegen Polio
ምስል፦ DW/S. Wegayehu

የልጅነት ልምሻ ከአፍሪቃ ተወገደ

This browser does not support the audio element.

     
የልጅነት ልምሻ ወይም ፖሊዮ ከመላዉ አፍሪቃ ሙሉ በሙሉ መጥፋቱን የዓለም ጤና ድርጅት ትናንት አረጋገጠ።ድርጅቱ እንዳለዉ የልጅነት ልምሻ አፍሪቃ ዉስጥ ለመጨረሻ ጊዜ የታየዉ የዛሬ አራት ዓመት ግድም ናጄሪያ ዉስጥ ነበር።ከዚያ በኋላ በተከታታይ በተሰጠዉ ክትባት በየዓመቱ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ለአካለ ጎዶሎነት ከሚዳርገዉ በሽታ አፍሪቃ ነፃ መሆንዋ ተረጋግጧል።ይሁንና በሽታዉን የሚያመጣዉ ተሕዋሲ ዳግም ሊያንሰራራ ስለሚችል ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት የጤና ባለሙያዎች ይመክራሉ።የልጅነት ልምሻ አሁንም አፍቃኒስታንና ፓኪስታን ዉስጥ መኖሩን የዓለም ጤና ድርጅት አስታዉቋል።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW