1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ኢትዮጵያዉን ከሱዳን ተባረሩ

ዓርብ፣ መጋቢት 3 2013

የሱዳን በተለይም ገዳሪፍ ግዛት የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እንደሚሉት ዉዝግቡ ከተካረረ ወዲሕ የሱዳን ታጣቂዎች ኢትዮጵያዉያንን እየደበደቡና እየዘረፉ ከየሚኖሩበት አካባቢ እያበረሯቸዉ ነዉ።

Grenzstreit zwischen Äthiopien und Sudan I Metema Stadt
ምስል፦ Alemenew Mekonnen/DW

ከሱዳን የተባረሩ ኢትዮጵያዉያን

This browser does not support the audio element.

                   
ኢትዮጵያና ሱዳን በድንበር ግዛት ይገባኛል ሰበብ የገጠሙት ዉዝግብ ዳፋዉ ሱዳን ለሚኖሩ ኢትዮጵያንም እየተረፈ ነዉ።የሱዳን በተለይም ገዳሪፍ ግዛት የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እንደሚሉት ዉዝግቡ ከተካረረ ወዲሕ የሱዳን ታጣቂዎች ኢትዮጵያዉያንን እየደበደቡና እየዘረፉ ከየሚኖሩበት አካባቢ እያበረሯቸዉ ነዉ።የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር እንዳስታወቀዉ ባለፉት ወራት በሱዳን ታጣቂዎች የተባረሩ 230 ኢትዮጵያዉያን ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ተገድደዋል።ከተባረሩት ኢትዮጵያዉያን አንዳዶቹ እስከ 30 ዓመት  ድረስ ሱዳን ዉስጥ የኖሩ ናቸዉ።መተማ-ዮሐንስ በተባለዉ አካባቢ የሠፈሩት ተባራሪዎች የመጠለያና የመሰረታዊ አገልግሎቶች ችግር እንዳለባቸዉ አስታዉቀዋልም።የባሕርዳሩ ወኪላችን ዓለምነዉ መኮንን እንደዘገበዉ ከሱዳን የተባረሩት አብዛኞቹ የአማራ ተወላጆች ናቸዉ።

ዓለምነዉ መኮንን

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW