ኢትዮጵያውያን ስለ ተሳናባቿ መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ምን ይላሉ?
እሑድ፣ መስከረም 16 2014ማስታወቂያ
"ፖለቲካን እንደ ሳይንቲስት ይመለከታሉ" የሚባልላቸው መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ሥልጣን ላይ በቆዩባቸው አስራ ስድስት አመታት በተክለ-ስብዕናቸውም ይሁን በአመራር ክህሎታቸው አድናቆትን አትርፈዋል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለለኝ እና አቶ መለስ ዜናዊን ጨምሮ ከበርካታ አገራት መሪዎች ጋር ድንበር ለሚሻገሩ ችግሮች መፍትሔ ፍለጋ ተወያይተዋል።
ከቅርቡ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና የከባቢ አየር ለውጥ ጉዳዮች ይጠቀሳሉ። የተሻለ ዕድል ፍለጋ ከአፍሪካ እና የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ወደ አውሮፓ የሚጓዙ ሰዎች መብዛት ቀውስ ሲፈጥር ለመፍትሔ የጀርመንን በር የከፈቱት አንጌላ ሜርክል ናቸው። ለአፍሪካውያን የሥራ ዕድል የሚፈጥር ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ የተባለ መርሐ-ግብር ተቀርጾ ተግባራዊ ለማድረግ የተሞከረውም በእርሳቸው የሥልጣን ዘመን ጀርመን የቡድን 20 አገራት ፕሬዝደንት ሳለች ነው። እነዚህ ጉዳዮች አንዳንዶቹ ለኢትዮጵያውያን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪም የቀረቡ ናቸው። ኢትዮጵያውያን ስለሜርክል ሲጠየቁም በግንባር ቀደምትነት ያነሷቸዋል።
ስዩም ጌቱ
እሸቴ በቀለ
ሒሩት መለሰ