ኢትዮጵያ ሱዳንና ግብፅ የናይል ወንዝ ዉዝጋባቸዉን ይፍቱ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 17 2011ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ የሕዳሴዉ ግድብ ግንባታ መጀመርን ተከትሎ ኢትዮጵያ ሱዳንና ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ የገቡበትን ዉዝግብ ሊፈቱ የሚገባ መሆኑን « ክራይሲስ ግሩፕ» የተባለዉ በግጭቶች ላይ የሚሰራዉ ድርጅት በቅርቡ ይፋ ያደረገዉ ዘገባ አስታዉቋል። የአባይ ወንዝ ኢትዮጵያን ለቆ ሲወጣ ናይል የሚባል ሲሆን 84 % የሚሆነዉ የናይል ወንዝ ዉኃ የሚፈልቀዉ ደግሞ ኢትዮጵያ ዉስጥ ነዉ። ግብፅ 90 % የሆነዉን ንፁሕ የዉኃ ፍላጎትዋን የምታሟላዉ ከናይል ወንዝ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም ግብፅ ማንኛዉም በአባይ ወንዝ ላይ የሚዘረጋ የኃይል ማመንጫ የግብፅን ዉኃ ፍሰት እንዳይቀንሰዉ ትሰጋለች። የብራስልሱ ወኪላችን ኢትዮጵያ ግብፅ እና ሱዳን የናይል ዉኃ አጠቃቀምን በተመለከተ « ክራይሲስ ግሩፕ» የተባለዉ በግጭቶች ላይ የሚሰራዉ ድርጅት ምሁርን አነጋግሮ ዘገባ አዘጋጅቶአል።
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ