ድጋፍ ደብረ ብርሃን ለሚገኙ ተፈናቃዮች
ረቡዕ፣ ኅዳር 15 2014ማስታወቂያ
በደብረ ብርሃን ከተማ ተጠልለው የሚገኙ ጦርነት ያፈናቀላቸው ዜጎች ቁጥር ከ441 ሺህ መብለጡን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማሕበር ገለፀ። ማሕበሩ በከተማው ለሚገኙ ተፈናቃዮች የምግብ፣ የመድኃኒት ፣ የማረፊያ እና ሌሎች ድጋፎችን እየሰጠ መሆኑን ገልጿል። ቀይ መስቀል በትግራይ ክልል የሚያደርገው ድጋፍ በክልሉ ባሉ ቅርንጫፍ ቢሮዎቹ ሳይቋረጥ መቀጠሉንም ተናግሯል። ሕወሓት በኃይል በያዛቸው የአማራ ክልል ከተሞች አሁንም ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የገለፀው ማህበሩ ሆኖም በእነዚህ አካባቢዎች ያለው የፀጥታ ሥጋት በሥራ ላይ እክል መፍጠሩንም ለዶይቼ ቬለ ነግሯል።የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ከሰሜኑ ኢትዮጵያ በተጨማሪ በወለጋ እና በመተከል በፀጥታ ችግር ፣ በቦረና በድርቅ ለጉዳት የተጋለጡትን እያገዘ እንደሚገኝና ይህንንም ለማጠናከር ሕዝብ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ