1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ተቃውሞ በኢትዮጵያ

እሑድ፣ ነሐሴ 8 2008

መንግሥት ሰልፎችን ለማስቆም ጠንካራ እርምጃዎች ቢወስድም የተቃውሞ ሰልፍ እንዲደረግ የሚደረገው ጥሪ እንደቀጠለ ነው ። ይህ ወዴት ያመራል ? ተጨማሪ የሰዎች ህይወት እንዳይጠፋስ ምን መደረግ አለበት ?

Äthiopien Protest
ምስል Reuters/T. Negeri

ኢትዮጵያ ፣ተቃውሞውና የመንግሥት እርምጃ

This browser does not support the audio element.

ባለፈው ሳምንት በአማራ እና በኦሮምያ ክልሎች በተካሄዱ ሰላማዊ ሰልፎች የሰዎች ህይወት መጥፋቱ ሰልፈኞች ለከባድ ድብደባ መዳረጋቸው እና መታሰራቸው አሁንም እያነጋገረ ነው። አጀማመራቸው ሰላማዊ የነበረው እነዚህ ሰልፎች መጨረሻቸው ግድያ ድብደባ እና እሥራት መሆኑ ልዩ ልዩ ጥያቄዎችንም እያስነሳ ነው ። ሰልፎቹን በውጭ ጠላት ኃይሎች የተደረጀ » የሚለው መንግሥት ሰላማዊ ተቃውሞ ለማካሄድ አደባባይ በወጡ ሰዎች ላይ ከመጠን ያለፈ እርምጃ ነው የወሰደው ተብሏል ። ይህን የሚያጣሩ ታዛቢዎችን እንድታስገባ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ኢትዮጵያን ጠይቋል ። መንግሥት ሰልፎችን ለማስቆም ጠንካራ እርምጃዎች ቢወስድም የተቃውሞ ሰልፍ እንዲደረግ የሚደረገው ጥሪ እንደቀጠለ ነው ። ይህ ወዴት ያመራል ? ተጨማሪ የሰዎች ህይወት እንዳይጠፋስ ምን መደረግ አለበት ? የዛሬው እንወያይ የሚያነሳቸው ነጥቦች ናቸው ።ሙሉውን ውይይት የድምፅ ማዕቀፉን በመጫን ተከታተሉ ።

ኂሩት መለሰ

ልደት አበበ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW