ኢትዮጵያ፣ ተቃውሞ እና ኢንቬስትመንት
እሑድ፣ መስከረም 8 2009ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ካለፉት ዓመታት ወዲህ ጠንካራ የኤኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኗን መንግሥት እየገለጸ ነው። ለዚሁ እድገትም የአገር ውስጥና የውጭ ባለወረቶች መሰማራት ከፍተኛ ድርሻ እንዳበረከተ ይገልጣል። ይሁንና፣ ካለፉት በርካታ ሳምንታት ወዲህ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የታየው ተቃውሞ እና ግጭት ከተለያዩ ዘርፎች ጎን፣ በኤኮኖሚው እንቅስቃሴም ላይ ተፅዕኖ ማስከተሉን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ይናገራሉ። ተቃውሞ እና ግጭቱ በወረት ፍሰት እንቅስቃሴ፣ በተለይም፣ በውጭው ኢንቬስትመንት ላይ ሊያሳርፈው የሚችለው ወይም ያሳረፈው ተፅዕኖ ሰሞኑን እያነጋገረ ነው።
ሙሉውን ውይይት ለማድመጥ ከታች የሚገኘውን የድምጽ ማጫወቻ ይጫኑ።
አርያም ተክሌ
ማንተጋፍቶት ስለሺ