1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ኢትዮጵያ ዉስጥ የቴክኒክና የሙያ ተማሪዎች ቁጥር እያሽቆለቆለ መሆኑ ተነገረ

ኢሳያስ ገላው
ረቡዕ፣ ግንቦት 27 2017

በተመሳሳይም በኦሮሚያ ክልልም አምቦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር ለሚ እንደሚገልጹት ለቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚወጣው ፖሊሲ በየጊዜው የሚቀያየርና ገና ያልተጠናቀቀ መሆን ለተማሪዎቹ ፍላጎት ማጣት ምክንያት ነው ይላሉ፡

«12ኛ ክልልን ካጠናቀቁ  በኋላ ተማሪዎች ወደ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ  ገብተው የመማር ፍላታቸው ዝቅተኛ ነው።» መምሕር ሰለሞን ፈንታው
ደሴ የሚገኘዉ የወይዘሮ ስሕን መታሰቢያ የፖሊቴክኒክ ትምሕርት ቤት።ምስል፦ Esayas Gelawe/DW

ኢትዮጵያ ዉስጥ የቴክኒክና የሙያ ተማሪዎች ቁጥር እያሽቆለቆለ መሆኑ ተነገረ

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ ዉስጥ የቴክኒክና የሙያ ትምህርት የሚያጠኑ ተማሪዎች ቁጥር እያሽቆለቆለ መሆኑ ተነገረ።የጥራት ችግርና ዘርፉን የሚቀላቀሉ ሰልጣኞች ዝቅተኛ ዉጤት ያላቸዉ ተማሪዎች መሆን ለዘርፉ ወጤታማ አለመሆን ምክኒያት ነዉ ይባላል።ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲሕ  ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ገቡተዉ የመማር ፍላጎት ያላቸዉ ተማሪዎች ቁጥር በእጅጉ እየቀነሰ ነዉ ተብሏል።የስራና ክሂሎት ሚንስቴር በበኩሉ አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ተማሪዎች በኮሌጆች ገቡተዉ  እየሰለጠኑ ነዉ ይላል።

ሰልጣኝ ተማራዎችን እያጡ የመጡ  የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በኢትዮጵያ 

በአማራ  ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ  አዞን  አስተዳደር የሚገኘውን የኬሚሴ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2-017 የትምህርት ዘመን ከ400 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማስተማር ስራ ቢጀምርም 50 ተማሪዎችን ብቻ ማግኘት እንደቻለ ነው  የኮሌጁ ዲን አቶ ሙክታር  ገዝሃኝ የሚናገሩት <እኛ በትምህርት ዓመቱ ወደ 400 ተማሪዎችን  ለመቀበል ነበር የሰራነው ግን ያገኘ ነው 50 ተማሪ ነው በዚህ ዓመት>  

በተመሳሳይም በኦሮሚያ ክልልም አምቦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር ለሚ እንደሚገልጹት ለቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚወጣው ፖሊሲ በየጊዜው የሚቀያየርና  ገና ያልተጠናቀቀ መሆን  ለተማሪዎቹ  ፍላጎት  ማጣት ምክንያት  ነው ይላሉ፡፡<ፖሊሲያችን ከባድ ክፍተት አለበት ለምሳሌ፡- ዘንድሮ ምትቀበላቸው ተማሪዎች አሉ እነዚያ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተምረው ሳይጨርሱ ሌላ  ፖሊሲ እንደገና እንተገብርባቸዋለን ገና ተሞክሮ አላለቀም ፖሊሲያችን>

በወ/ሮ ሲህን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅመምህር የሆኑት አቶ ሰለሞን ፈንታው በበኩላቸው 12ኛ ክልልን ካጠናቀቁ  በኋላ ተማሪዎች ወደ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ  ገብተው የመማር ፍላታቸው ዝቅተኛ ነው ይላሉ።<12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ 20/80 ይመጣሉ  ብለን ነው እ ምንጠብቀው 80/100ዎቹ ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች  ይገባሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው ከዚያ ውስጥ 80/100 መንግስታዊ በሆኑ ኮሌጆች ይገባሉ ተብሎ  ቢጠበቅም 20/100 እንኳን የሚገባ የለም፡፡>

የመምህራን ያለስራ መቀመጥ

በፖሊ ቴክኒክ  ኮሌጅ ገብተው የሚማሩ  ተማሪዎች በቁጥር ዝቅተኛ መሆንና |የዘርፉ በተማሪዎች ተመራጭ አለመሆን ለበርካታ መምህራን ስራ መፍታት ምክንያት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ <አንዳንድ  ኮሌጆች ተዘግተዋል አሁን አካባቢን መሰረት ያደረጉ ስልጠና ስለሆነ የምንሰጠው ከዚያ ውጭ ባለው እኛም ተማሪ ቢመጣ አንቀበልም መምህራኖቹ ግን ያው እንደትርፍ ተቀምጠዋል እኛም ለክልል አሳውቀናል፡፡>

አሁን በፖሊ ቴክኒክ  ኮሌጅ ገብተው የሚማሩ ተማሪዎች ስልጠና ከጀመሩ በኋላ ያቋጣሉ  የሚለው ተማሪ ሀይለሚካኤል እረታ ጥራት ያላቸው መምህራን ማግኘትና የተግባ ር ስልጠናዎቹ ያልተሟሉ አለመሆን ለተማሪዎቹ ማቋረጥ ምክንያት ነው ይላል፡፡ <እኛ ክፍል ስንጀምር 30 ተማሪዎች ነበርን ከዚያ 12 ቀረን የምትፈልገው ነገር ተሟልቶ የሚሰጥ ተቋም አታገኝም ከመምህራን ጀምሮ ጥራት ያለው ሊጎድል ይችላል፡፡>

በአማራ ክልል 12ተኛ ክፍልን የሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ማነስ

 

በአማራ ክልል ከተማሪዎች ፍላት ማጣት ይልቅ  በወቅቱ  በክልልሉ ያለው የሰላም እጦት የተማሪዎች መደበኛ ትምህርትን ተከታትሎ አለማጠናቀቅ አንዳንድ  ኮሌጆች ተማሪዎች ለማጣታቸው ምክንያት መሆኑን አቶ ሙላው ልመነህ የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ የተቋት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ይናገራሉ፡፡<12ኛ ክፍል የሚጨርሰው ሰልጣኝ ቁጥር እንደሚታየው እንደሀገር ዝቅተኛ ቁጥር ነው በዚህ በአማራ ክልል ባሉ ገጠር ወረዳዎች አሁን  ላይ 12ኛን ክፍል የሚማሩ ተማሪዎችን ስናይ የመቀነስ አዝማሚያ አለው>

ወደ ፖሊቴክኒክ ትምሕርት ቤት ገብተዉ ለመማር የሚፈልጉ ተማሪዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መሆኑን፣ መምሕራንና ተማሪዎች ይናገራሉ።ምስል፦ Esayas Gelawe/DW

የስራ እና ክህሎት ሚኒስተር በበኩሉ አሁን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚታየው የመደበኛ ስልጠና ተማሪዎች መቀነስ የዘርፍ  መቀየር ነው እንጅ ተማሪዎቹ በአጫጭር ስልጠናዎች እየበቁ ነው  ይላሉ አቶ ሙህዲን አባሞጋ በሚኒስቴሩም የቴክኒክና ሙያ ዘርፈ የተቋማት  አቅም ግንባታ መሪ ስራ አስፈጻሚ<የፍላጎት ወይም የዘርፍ መቀየር ነው እንጅ በአጠቃላይ የሰልጣኝ ቁጥር መቀነስ አይደለም የመደበኛ ሰልጣኝ ይን ያህል ቢሆንም የአጫጭር ስልጠና ሰልጣኖች የዚህን 3እና 4 እጥፍ ይኖራል፡፡>

በተለይም ተማሪዎች በመደበኛ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች  ገብተው መማር ያለመፈለግ ለበርካታ መምህራን ከስራ ውጭ  መሆን ምክንያት ሁነዋል ስንል የጠየቅናቸውን አቶ ሙህዲን አባጋሞ በወቅቱ ይህንን አይፈቅድም ብለዋል፡፡  <እኛ አሁን ባለን በየተቋቱ የሚሰራው የረፎርም እንቅስቃሴ ሰዎችን ስራ አስፈትቶ ያስቀምጣል የሚል ግምት የለንም በጣም የተለያዩ ኢንሸቲቮች በየተቋቱ እየተሰሩ ነው» ያሉት፡፡

ኢሳያስ ገላዉ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ

 

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW