ኢትዮጵያ፣ የ 2007 ምኞትና ተስፋ
እሑድ፣ መስከረም 11 2007ማስታወቂያ
ትዝታ ሌላ ፣ በኢትዮጵያ ሕዝብ የአብሮነት ስሜት ፤ መቻቻል፤ የባህል መወራረስ፣ ለዘመናዊ አስተዳደር ጠቃሚ በሆኑ ባህላዊ እሴቶች ላይ ሐሳባቸውን አካፍለውን እንደነበረ ይታወስ ይሆናል። በዛሬው በሁለተኛውና የመጨረሻ ክፍል ውይይታችን ትምህርት፣ ምርምርና ወጣቶች፣ እንዲሁም ዘንድሮ የሚካሄደው ምርጫና ፣ እንዴት ቢሠራ ስለሚሰምርበት ሁኔታ ተወስቷል።
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ በአመዛኙ የወጣቶች ሀገር ናት ። በ 10ና በ 24 ዓመት የዕድሜ ዕርከን ላይ የሚገኘው እንኳ 30,5 ሚሊዮን ገደማ መሆኑ ነው የሚነገረው። 35 ከመቶ መሆኑ ነው። ዕድሜው ከ 40 ዓመት በታች የሆነውን ትውልድ ከጨመርን ደግሞ ፣ መጠኑ የትና የት ነው! ታዲያ ይኸው ወጣት ትውልድ አገር ገንቢ ዜጋ መሆን የሚችለው በምን ዓይነት ትምህርት ቢታነጽ ነው?
ተክሌ የኋላ
አዜብ ታደሰ