ኢዴፓ ለዘብተኛ ፓርቲዎችን መቀላቀሉ
ረቡዕ፣ ግንቦት 1 2004ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በምህፃሩ ኢዴፓ፤ አራምደዋለሁ ባለዉ የለዘብተኛ(ሊበራል) ፍልስፍና የአፍሪቃ ብሎም የዓለም ተመሳሳይ ፍልስፍና አራማጅ ፓርቲዎችን መቀላለቁን አመለከተ። ፓርቲዉ አዲስ አበባ ላይ ለሁለት ቀናት ባካሄደዉ ስብሰባ ከአፍሪቃ አገራት ከተዉጣጡ 14 ተመሳሳይ ፓርቲዎች ጋ ተወያይቷል። በወቅቱም በስልጣን ድልድል፤ ምርጫ፤ ሃሳብን ነፃነት በመግለፅና በፖለቲካ ፓርሪዎች መብት እንዲሁም በመልካም አስተዳደር ላይ ተግባራዊ ሊሆኑ ይገባል በሚሉት ነጥቦች ከስምምነት ደርሰዉ ተፈራርመዋል። ወኪላችን
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ የፓርቲዉን ሊቀመንበር አነጋግሮ ቀጣዩን ዘገባ አድርሶናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሰ