1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የ«ኤስ ፔ ዴ» እጩ ተወዳዳሪ

ረቡዕ፣ ጥር 17 2009

የጀርመን ሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ፣ የ«ኤስ ፔ ዴ»  መሪ፣ ምክትል መራሔ መንግሥት እና የኤኮኖሚ ሚንስትር ዚግማር ጋብርየል በሚቀጥለው መስከረም ወር በሚካሄደው ፌዴራዊ ምክር ቤታዊ ምርጫ ላይ ፓርቲያቸውን በመወከል በመራሒተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል አንፃር እንደማይወዳደሩ ትናንት አስታወቁ።

Deutschland Martin Schulz bei der SPD Bundestagfraktion
ምስል picture alliance/dpa/K. Nietfeld

Ber. Berlin(SPD Kanzlerkandidat) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

በሳቸው ፈንታ ፓርቲውን ለድል የማብቃት እድላቸው የተሻለ ነው ያሏቸውን ጓዳቸውን እና የቀድሞው የአውሮጳ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ማርቲን ሹልስ  የ«ኤስ ፔ ዴ»  እጩ ተወዳዳሪ ሆነው እንዲቀርቡ ሀሳብ አቅርበዋል። ጋብርየል የእጩ ተወዳዳሪውን ጥያቄ መልስ በሳምንቱ መጨረሻ ይካሄዳል በተባለ የፓርቲያቸው ስብሰባ ላይ ይፋ ያደርጉታል ተብሎ እየተጠበቀ ሳለ፣ ትናንት ድንገት ብዙዎች ከጠበቁት ለየት ያለ ውሳኔ መድረሳቸውን ማሳወቃቸው የፓርቲ ጓዶቻቸውን እና አባላትን ብቻ ሳይሆን በሃገሪቱ ብዙዎችን  አስገርመዋል።

ይልማ ኃይለሚካኤል

አርያም ተክሌ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW