1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 እልባት ያላገኘው የስጳኝ እና የካታላን ውዝግብ

ሰኞ፣ ጥቅምት 6 2010

የካታላን ራስ ገዝ አስተዳደር ራሱን ከስጳኝ  ለመገንጠል በሚለው ጥያቄ ላይ ከ16 ቀናት በፊት  ባካሄደው ሕዝበ ውሳኔ ሰበብ ከማዕከላይ መንግሥቱ ጋር  የተፈጠረው ውዝግብ አሁን እየተባባሰ መጥቷል።

Spanien Carles Puigdemont Premier der Regionalregierung
ምስል Reuters/I. Alvarado

አጣብቂኝ ሁኔታ ላይ የሚገኙት የካታላን መሪ

This browser does not support the audio element.

የስጳኝ ማዕከላይ መንግሥት የካታላን መሪ ካርለስ ፕዊጂዴሞንት ባለፈው ሳምንት ለምክር ቤት ባሰሙት ንግግራቸው ነፃነት አውጀው መሆን አለመሆናቸውን በግልጽ እንዲያሳውቁ የሰጣቸው ቀነ ገደብ ፕዊጂዴሞንት መልስ ሳይሰጡ ዛሬ አብቅቷል። የካታላን መሪ ካርለስ ፕዊጂዴሞንት  ዛሬ መልሳቸውን ያሳውቃሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ እሳቸው ግን ከማዕከላዩ መንግሥት ጋር ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት ንግግር እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ነው የላኩት። በዚህም የተነሳ ስጳኝ ቀነ ገደቡን እስከ ሀሙስ ማራዘሟ ተሰምቷል። ፕዊጂዴሞንት የግዛቱን ነፃነት ማወጅ አለማወጃቸውን በግልጽ ያላሳወቁበትን ምክንያት እና የስጳኝ መንግሥት በግዛቱ እና በመሪዎቹ አንጻራቸው ሊወስደው ይችላልል የሚባለውን ርምጃ በተመለከተ የብራስልሱን ወኪላችን ገበያው ንጉሤን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ኂሩት መለሰ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW