እልባት ያላገኘው የስጳኝ እና የካታላን ውዝግብ
ሰኞ፣ ጥቅምት 6 2010ማስታወቂያ
የስጳኝ ማዕከላይ መንግሥት የካታላን መሪ ካርለስ ፕዊጂዴሞንት ባለፈው ሳምንት ለምክር ቤት ባሰሙት ንግግራቸው ነፃነት አውጀው መሆን አለመሆናቸውን በግልጽ እንዲያሳውቁ የሰጣቸው ቀነ ገደብ ፕዊጂዴሞንት መልስ ሳይሰጡ ዛሬ አብቅቷል። የካታላን መሪ ካርለስ ፕዊጂዴሞንት ዛሬ መልሳቸውን ያሳውቃሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ እሳቸው ግን ከማዕከላዩ መንግሥት ጋር ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት ንግግር እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ነው የላኩት። በዚህም የተነሳ ስጳኝ ቀነ ገደቡን እስከ ሀሙስ ማራዘሟ ተሰምቷል። ፕዊጂዴሞንት የግዛቱን ነፃነት ማወጅ አለማወጃቸውን በግልጽ ያላሳወቁበትን ምክንያት እና የስጳኝ መንግሥት በግዛቱ እና በመሪዎቹ አንጻራቸው ሊወስደው ይችላልል የሚባለውን ርምጃ በተመለከተ የብራስልሱን ወኪላችን ገበያው ንጉሤን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ገበያው ንጉሤ
አርያም ተክሌ
ኂሩት መለሰ