ኦፌኮ እና ኦነግ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ
ሰኞ፣ ጳጉሜን 5 2010ማስታወቂያ
የኦሮሞ ፌድራሊስት ኮንግረስ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታወቁ። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ እንደተናገሩት ሁለቱ ፓርቲዎች የኦሮሞ ሕዝብ ድምፅ እንዳይከፋፈል በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል። መቀመጫውን በኤርትራ አድርጎ የነበረው እና በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ መወሰኑን አስታውቋል። የኦነግ መሪ አቶ ዳውድ ኢብሳ በመጪው መስከረም 5 ቀን 2011 ዓ.ም. ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
እሸቴ በቀለ
ኂሩት መለሰ