የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት እርምጃ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 1 2012ማስታወቂያ
ሳዑዲ አረቢያ የኮሮና ተህዋሲን ሥርጭት ለመከላከል የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው።በተለያዩ የሳዑዲ አረብያ እስር ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎች በኮሮና ምክንያት በምህረት እየተለቀቁ ነው።ከመካከላቸው 1000የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል። ታራሚዎቹን ከሳውዲ ወደ ኢትዮጵያ ማጓጓዙ በኢትዮጵያ እና በሳዑዲ አረብያ መንግሥታት ስምምነት እየተከናወነ መሆኑን የጅዳ ቆንስል መ/ቤት የበላይ አምባሳደር አብዱ ያሲን ለዶቼቬለ ተናግረዋል። በግምት ወደ 6000ያህል የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ወህኒ ቤቶች አሉ ተብሎ ይገመታል።
ነቢዩ ሲራክ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ