1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ከታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውን ምን ይጠብቃሉ?

ሥዩም ጌቱ
ማክሰኞ፣ ጳጉሜን 4 2017

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የገነባችውን ታላቁን የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ በዛሬው ዕለት ስታስመርቅ ኢትዮጵያውን በተለያዩ የመገናኛ ብዙኀን አማራጮች በቀጥታ ተመልክተውታል።

የኅዳሴ ግድብ ምረቃ
የኅዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱ ለዶቼ ቬለ አስተያየት የሰጡትን ወገኖች እንዳስደሰተ ነው የተናገሩ። ምስል፦ AP Photo/picture alliance

ከታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውን ምን ይጠብቃሉ?

This browser does not support the audio element.

 

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የገነባችውን ታላቁን የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ በዛሬው ዕለት ስታስመርቅ ኢትዮጵያውን በተለያዩ የመገናኛ ብዙኀን አማራጮች በቀጥታ ተመልክተውታል። ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ በርካታ ከተሞች ውስጥ የግድቡን መመረለቅ ብስራት ተከትሎ ሕዝብ ወጥቶ ደስታውን በስፋት ሲገልጽ የተስተዋለባቸው ቦታዎችም ጥቂት አይደሉም።

ለመጠናቀቅ ድፍን 14 ዓመታትን የፈጀው ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ብዙ አከራካሪ የጂኦፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ አውድ ፈተና ሜዳም ሆኖ ቆይቷል። ኢትዮጵያ በራሷ ዜጎች ተሳትፎ የገነባችው የ5 ቢሊየን ዶላር ግድም ፕሮጀክት ዛሬ ተጠናቆ ለምረቃ የበቃበት ምዕራፍ ላይ ከመድረሱ በፊት በርካታ ዲፕሎማሲያዊ ፈተናዎችን ሲያስተናግድም ዜጎችም በተለያየ መልኩ ተሳትፏቸውን ሲያረጋግጡ ነበር። አሁን ብዙ ተስፋ የተጣለበት ግድብ በይፋ ተመርቋል፤ ዜጎች ከግድቡ የትኞቹን ትሩፋቶች ይጠብቃሉ? ከኤሌክትሪክ አቅርቦት ጀምሮ አጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ እመርታን ማግኘት ከግድቡ መጠናቀቅ የሚጠበቁ እንደሆነም ተመላክቷል።

ሥዩም ጌቱ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW