ከተራዘመው የኢሕአዴግ ስብሰባ ምን ይጠበቃል?
ዓርብ፣ መጋቢት 7 2010ማስታወቂያ
ቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንሥትር ማን ሊኾን ይችላል? በርካቶች በተደጋጋሚ ጊዜያት የጠየቁት ኾኖም ከመላ ምት ባሻገር እስካሁን ኹነኛ መልስ ያላገኙለት ጥያቄ ነው። ከተጠበቀው በላይ ከተራዘመው የኢሕአዴግ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ በኋላ እንደ ደንቡ ሊቀ-መንበሩን እና ጠቅላይ ሚንሥትሩን የሚሰይመው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ምን ሊወስን እንደሚችል በውል ዐይታወቅም። ኢሕአዴግ ከድርጅቱ ሊቃነ-መናብርት ውጪ ጠቅላይ ሚንሥትር ሊሰይም እንደሚችልም በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሣይንስና እና ፍልስፍና ከፍተኛ መምህር አቶ ግደይ ደገፉ ግምታቸውን ሰጥተዋል። ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝሩን ከአዲስ አበባ ልኮልናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ሸዋዬ ለገሰ