ከእስር የተፈቱት የሳዑዲ ልዑል ተናገሩ
ረቡዕ፣ መጋቢት 12 2010ማስታወቂያ
ልዑሉ ከእስር ከተፈቱ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ከብሉምበርግ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ በደረሰባቸዉ የያዙትም ቂም እንደሌለ እና ለንጉሱም ሆነ ለአልጋ ወራሹ ይቅርታ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ዎል ስትሬት ጆርናልን ጨምሮ በርካታ መገናኛ ብዙሃን ስድስት ሚሊየን ዶላር ከፍለው ነው የተለቀቁት ብለው ቢዘግቡም እሳቸዉ ግን ምንም የከፈሉት እንደሌለ አጽንኦት ሰጥተዋል። በግላቸው ከንጉሱም ሆነ ከአልጋ ወራሹ ጋር ሚስጢራዊ ስምምነት ማድረጋቸውን ይፋ ያደረጉት ልዑል ወሊድ ቢንጥላል ዝርዝር ሁኔታዎችን ለማብራራት ግን እንደማይፈልጉ ነዉ ያሳወቁት። ከሪያድ ስለሺ ሽብሩ ከሪያድ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።
ስለሺ ሽብሩ
ሸዋዬ ለገሠ
ኂሩት መለሰ