1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከ60 በላይ ሲቪል ማሕበራት የመቀሌ ጉብኝት

ሰኞ፣ ጥር 15 2015

ከ60 በላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት እንዲሁም የሌሎች ተቋማት ተወካዮች ዛሬ በመቐለ ተገኝተው ከትግራይ ክልል ሲቪል ተቋማት አመራሮች ጋር ተወያዩ። የተቋማቱ የዛሬ የመቐለ ጉብኝት በጦርነቱ ምክንያት ለሁለት ዓመት ተቋርጦ የቆየ ማእከላቸው አዲስአበባ እና መቐለ ያደረጉ የሲቪል ተቋማት ግንኙነት ዳግም ያስጀመረ ተብሎለታል።

Äthiopien Tigray l Treffen der äthiopischen Zivilorganisationen in Mekele
ምስል Million Hailesilassie/DW

ሲቪል ተቋማት ግንኙነትን ዳግም ያስጀመረ

This browser does not support the audio element.

ከ60 በላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት እንዲሁም የሌሎች ተቋማት ተወካዮች ዛሬ በመቐለ ተገኝተው ከትግራይ ክልል ሲቪል ተቋማት አመራሮች ጋር ተወያዩ። የተቋማቱ የዛሬ የመቐለ ጉብኝት በጦርነቱ ምክንያት ለሁለት ዓመት ተቋርጦ የቆየ ማእከላቸው አዲስአበባ እና መቐለ ያደረጉ የሲቪል ተቋማት ግንኙነትን ዳግም ያስጀመረ ተብሎለታል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ምክርቤት ያስተባበረው እና በርካታ የኢትዮጵያ ሲቪል ተቋማት የተሳተፉበት ዛሬ በመቐለ ከትግራይ አቻ ተቋማት ጋር የተደረገው ውይይት እና የስራ ጉብኝት በጦርነቱ ምክንያት ለሁለት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የሁለቱ ወገን የሲቪል ተቋማት ግንኙነት ዳግም ያስጀመረ ተብሎለታል። 61 የተለያዩ የኢትዮጵያ ሲቪል ተቋማት ተወካዮች ከአዲስአበባ መቐለ በመምጣት በትግራይ ካሉ ከ72 በላይ የሲቪል ተቋማት ተወካዮች ጋር የተገናኙበት የዛሬው መድረክ፥ የተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች የሚወክሉ ተቋማት ግንኙነት ከማስቀጠል በተጨማሪ በጦርነቱ ምክንያት እንቅስቃሴያቸው ተገትቶ የነበሩ ድርጅቶች ዳግም ስራ የሚጀምሩበት ሁኔታ ለመፍጠር፣ አጋርነት ለማሳየት እንዲሁም የሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦት ስራዎች ለማጠናከር ያለመ መሆኑ በአዘጋጆቹ በኩል ተገልጿል።

ከ60 በላይ የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት እንዲሁም የሌሎች ተቋማት ተወካዮች በመቐለምስል Million Hailesilassie/DW

በሲቪል ተቋማቱ የመቐለ ጉብኝት ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ምክርቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሄኖክ መለሰ፣ በጦርነቱ ምክንያት የተጎዳ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በማጠናከሩ ረገድ ሲቪል ተቋማት ከፍተኛ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ይህ ሚና ለመወጣት በትግራይ ካሉ አቻ ማሕበራት ጋር ይሰራል ብለዋል።
የትግራይ ሲቪል ተቋማት ሕብረት ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ በርሃ በበኩላቸው የ61 ተቋማቱ የመቐለ ጉብኝት እና ከመሰል ተቋማት ያደረጉት ውይይት ፍርያማ ነበር ያሉት ሲሆን በተለይም በሰላም ግንባታ፣ ሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ላይ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ዛሬ በመቐለ የተገኙት የ61 ሲቪል ተቋማት ተወካዮቹ በከተማው የሚገኝ የተፈናቃዮች መጠልያ ጣብያ እና ፌስቱላ ማእከላት ጎብኝተዋል።

 

ሚሊዮን ኃይለሥላሴ 

አዜብ ታደሰ 

ታምራት 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW