1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ኬንያ በተከሰተ ድርቅ ከ 200 በላይ ዝሆኖች ሞቱ

ዓርብ፣ ጥቅምት 25 2015

በኬንያ በተከሰተዉ ከፍተኛ ድርቅ ከ200 በላይ ዝሆኖችና በመቶዎች የሚቆጠሩ የሜዳ አህዮች እንዲሁም ሌሎች የዱር አዉሬዎች መሞታቸዉን የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚንስትር ዛሬ ገለፀ። ይህ ድርቅ ያስከተለዉ ቀዉስ በኬንያ ወደ ግማሽ ቆዳ ስፋት የሚህል ክልልን እና ከ 50 ሚሊዮን ህዝቦቿ መካከል ቢያንስ አራት ሚሊዮን ህዝብን እንደተጎዳ ተነግሯል።

Kenia | Wildtiere leiden unter anhaltender Dürre
ምስል፦ R. de Haas/blickwinkel/AGAMI/picture alliance

ከአራት አስርት ዓመታት ወዲህ በኬንያ በተከሰተዉ ከፍተኛ ድርቅ ከ200 በላይ ዝሆኖችና በመቶዎች የሚቆጠሩ የሜዳ አህዮች እንዲሁም ሌሎች የዱር አዉሬዎች መሞታቸዉን የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚንስትር ዛሬ ገለፀ። ይህ ድርቅ ያስከተለዉ ቀዉስ በኬንያ ወደ ግማሽ ቆዳ ስፋት የሚህል ክልልን እና ከ 50 ሚሊዮን ህዝቦቿ መካከል ቢያንስ አራት ሚሊዮን ህዝብን በድርቅ እንደተጎዳ ተነግሯል።  የኬይና ቱሪዝም ሚኒስትር ፔኒና ማሎንዛ ዛሬ ዓርብ ናይሮቢ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ «ድርቁ የዱር እንስሳትን ለሞት ሲዳርግ፣ በአብዛኛው ዕፅዋት እንዲጠፉ ዳርጓል ፤ 14 የዱር አራዊቶች ዝርያ በድርቁ ክፉኛ ከስተዋል» ብለዋል።   በኬንያ፣ በሶማሊያና በኢትዮጵያ አራት ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ሳይዘንብ በመቅረቱ በአፍሪቃ ቀንድ ሃገራት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ለከፍተኛ ረሃብ ተጋልጠዋል። ድርቁ ባስከተለዉ ቀዉስ በኬንያ ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከብቶች ሞተዋል።  

በኬንያ ከፍተኛ ድርቅ የዱር አዉሬዎችን እየገደለ ነዉ ምስል፦ Andrew Wasike/AA/picture alliance

አዜብ ታደሰ 

ሸዋዬ ለገሠ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW