ኬንያ
ዓርብ፣ ሚያዝያ 22 2002ማስታወቂያ
ማንዴራ ፤ በኬንያ፤በኢትዮዽያና ሶማልያ ወሰኖች መጋጠሚያ ላይ የምትገኝ የኬንያ መንደር። ምናልባትም ማንዴራ 6 ሳምንታት የቀሩትንና በአፍሪካ ምድር ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄደውን የዓለም ዋንጫ ለማየት አትታደል ይሆናል። በሰሜናዊ ምስራቅ ኬንያ የሚገጘው የእስልምና ቡድን መሪዎች ማንዴራ ያሉ የቴሌቪዥንና የፊልም ማሳያ ቤቶች እንዲዘጉ ጥብቅ መመሪያ ሰጡ--ባለፈው ሰኞ። በእርግጥ ለማንዴራ ወጣቶች ጥሩ ዜና አልነበረም። የእስልምና መሪዎቹ ያስተላለፉት ውሳኔ በቅርቡ አልሸባብ የተሰኘው የሶማልያ አክራሪ ቡድን በደቡባዊ ሞቃዲሾ እየወሰደ ካለው እርምጃ ጋር ጊዜው መገጣጠሙ አነጋጋሪ አድርጎታል። ሮይተርስ የቡድኑን መሪ ሼክ ዳውድ ሼክ ማህሙድን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በማንዴራ አከባቢ እስላማዊ እሴቶችን ለመጠበቅ በሚል እርምጃው ተወስድዋል። በእስካሁንም 10 እንዲዘጉ ተደርገዋል።
መሳይ መኮንን
ተክሌ የኋላ