1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአማራ መስተዳድ እርምጃ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 15 2012

ዶክተር ፋንታሁን እንዳሉት ከዚህ በፊት  12 ሰዎችን ያሳፍሩ የነበሩ የከተማ ታክሲዎች  8 ሰዎችን ብቻ እንዲጭኑ፣ እስካሁን 3 ሰዉ ይጭኑ የነበሩ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ወይም ባጃጆች ደግሞ 2 ሰው ብቻ እንዲጭኑ መስተዳድሩ ደንግጓል

Dr. Fanta Mandefro
ምስል DW/A. Mekonnen

የኮሮና ተሕዋሲን ለመከላከል የአማራ ክልል ደንብ

This browser does not support the audio element.

             

የአማራ ክልላዊ መስተዳድር የኮሮና ተሕዋሲ ስርጭትን መከላከል ያስችላል ያለውን እርመጃ ደንብ አወጣ።ነዋሪዎቹ ግን የመስተዳድሩ አንዳድ ደንቦች ዉጤት ማምጣታቸዉን ይጠራጠራሉ።የአማራ  ምክትል ርዕሠ-መስተዳድር ፋንታ ማንደፍሮ ትናንት ማምሻውን ለጋጠኞች በሰጡት መግለጫ የክልሉ መንግስት ስርጭቱን ለመከላከል በተለይ  በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ አዲስ አሰራር ደንግጓል፡፡ዶክተር ፋንታሁን እንዳሉት ከዚህ በፊት  12 ሰዎችን ያሳፍሩ የነበሩ የከተማ ታክሲዎች  8 ሰዎችን ብቻ እንዲጭኑ፣ እስካሁን 3 ሰዉ ይጭኑ የነበሩ ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች ወይም ባጃጆች ደግሞ 2 ሰው ብቻ እንዲጭኑ መስተዳድሩ ደንግጓል።በክልሉ የሚገኙ መሸታ ቤቶች፤አዝማሪና ጭፈራ ቤቶች ከዛሬ ጀምሮ እንዲዘጉ ተወስኗልም።

 ዓለምነዉ መኮንን 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW