ኮፕ የደቡብ አፍሪቃ አዲሱ ፓርቲ7 ታኅሣሥ 2001ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 7 2001አራት ሺህ ተወካዮች የተሳተፉበት የአዲሱ የህዝብ ምክር ቤት የተባለው የደቡብ አፍሪቃ ፓርቲ ጉባኤ የቀድሞውን የደቡብ አፍሪቃ መከላከያ ሚኒስትር ሞሲዩዋ ሌኮቶን የፓርቲው ፕሬዝዳንት አድርጎ ሰይሟል ።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግሌኮቶምስል APማስታወቂያአዲሱ ፓርቲ ኮፕ በምርጫ ካሸነፈ የምርጫ ስርዓቱን እንደሚያሻሽል አስታውቋል ። በማሻሻያው መሰረትም ፕሬዝዳንቶች ና የክፍላተ ሀገራት ጠቅላይ ሚኒስትሮች እንዲሁም ከንቲባዎች በገዥው ፓርቲ ሳይሆን በቀጥታ በህዝብ እንዲመረጡ ይደረጋል ።