1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ወደ አፋር ክልል የተስፋፋው የትግራይ ጦርነት

ረቡዕ፣ ሐምሌ 14 2013

ስምንት ወራት የቆየውና አሁንም ያለዕልባት የቀጠለው የትግራዩ ጦርነት ሰሞኑን በአፋር ክልል በኩል ተስፋፍቶ 54 ሺህ ሰዎች ገደማ ማፈናቀሉን የአፋር ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኤጄንሲ አስታወቀ።

Karte Äthiopien englisch

በርካቶች ተፈናቅለዋል

This browser does not support the audio element.

ስምንት ወራት የቆየውና አሁንም ያለዕልባት የቀጠለው የትግራዩ ጦርነት ሰሞኑን በአፋር ክልል በኩል ተስፋፍቶ 54 ሺህ ሰዎች ገደማ ማፈናቀሉን የአፋር ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኤጄንሲ አስታወቀ። የኤጄንሲው ኃላፊ አቶ መሃመድ ሁሴን ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት በአፋር ዞን አራት ውስጥ በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ህወሃት ደርሷል ባሉት ጥቃት በተለይም በሁለቱ ክልሎች አዋሳኝ 8 ወረዳዎች ግማሽ ሚሊየን ያህል ህዝብን ድጋፍ ሊያስፈልገው እንደሚችል አረጋግጠዋል። በጦርነቱ ተጎድተው በየቦታው ለወደቁና ለተፈናቀሉ ዜጎች አስቸኳይ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አሁንም በቀጠለው ጦርነት መደናቀፉን ኃላፊው አክለዋል።

ስዩም ጌቱ 

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW