1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ወጣት ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ቴአትር ውስጥ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 8 2006

በኢትዮጵያ ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የቴአትር ጥበብ ዛሬም በአዲስ አበባ መድረኮች የተወሰነ ነው። ሙያውን የሚያስተምሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መበራከት ቢታይም ወጣት ተመራቂዎች ግን በሥራ ለመሠማራት እድሉን ማግኘት ከባድ ነው ሲሉ ይደመጣሉ።

73. Jahrestag äthiopische Patrioten
ምስል DW/A. T. Hahn

የቴአትር ባለሙያዎችና መምህራን በበኩላቸው ችግሮቹ ቢኖሩም ወጣቶች በግል ተቋማት ሥራዎቻቸዉን በማቅረብና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃንን በመጠቀም እውቀታቸውን ሊሳድጉ ራሳቸውን ተጠቃሚ ሊያደርጉ ይገባል ባይ ናቸው። ቲአትርን በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በማስተማር ቀዳሚው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴአትር ጥበባት ትምህርት ክፍል ነዉ።

ብሔራዊ ቴአትርምስል DW

ቀድሞ በትምህርት ክፍል ደረጃ የተቋቋመው የዛሬው የቴአትርጥበባት ትምህርት ቤት ባለፉት 35 ዓመታት ሙያውን ሲያስተምር ቆይቷል። ዛሬ ግን የወሎና የመቀሌ ዩኒቨርሲቲዎችም ማስተማር ጀምረዋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲም ተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ለመጀመርበዝግጅት ላይ ነው። የቲአትር ትምህርትን የተማሩ በዘርፉ መሥራት የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ቢመጣም ገበያው ግን እንዲህ ቀላል አይደለም። አንዱአለም ደጀኔ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቴአትርን የመጀመሪያ ዲግሪዉን የያዘ ወጣት ነው። አንዱአለም ቴአትርን ቢማርም በተማረዉ ሙያ ለመሠማራት ቀላል እንዳልሆነ ይናገራል። ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያድምጡ።

እሸቴ በቀለ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW