1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዉይይት፤ የኢትዮጵያ ጦርነትና የዲፕሎማሲዉ ጫና

እሑድ፣ ጥቅምት 14 2014

የዉይይቱ ተሳታፊዎች፣ አቶ ፍፁም አረጋ፣ በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር፤አቶ ጥሩነሕ ገምታ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) የፅሕፈት ቤት ኃላፊ፤አቶ ባይሳ ዋቅወያ፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያና የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣን ናቸዉ።

Äthiopien Soldaten der äthiopischen Nationalen Verteidigungskräfte (ENDF)
ምስል፦ AMANUEL SILESHI/AFP/Getty Images

«ድርድር ሽንፈት ዓይደለም፣ድርድር ስልጣኔ ነዉ----» አቶ ባይሳ ዋቅ ወያ

This browser does not support the audio element.

ትግራይ ዉስጥ የዛሬ ዓመት ጥቅምት የተጀመረዉ ጦርነት አድማሱን አስፍቶ የአማራና የአፋር ክልልሎችን አዳርሷል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ የተለያዩ ወገኖች እንደሚገምቱት ጦርነቱ በብዙ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት፣ በቢሊዮን ብር የሚገመት ሐብትና ንብረት አጥፍቷል።10 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ አፈናቅሏል፤ አሰድዷል፣ ለረሐብ አጋልጧልም።

 

ዉጊያ በሚደረግባቸዉና ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ በሚቆጣጠራቸዉ አካባቢዎች የመብራት፣የስልክ፣ የትራንስፖርት፣ የሕክምና አገልግሎት የለም።ትምሕርት፣እርሻና ንግድም ባብዛኛዉ ተቋርጧል ወይም ቀንሷል።ከትግራይና ከዋግ ሕምራ ዞን ሰሞኑን የተሰራጩ ዘገቦች እንደሚያመለክቱት ሕፃናትና አቅመ ደካሞች በረሐብና በመድሐኒት እጦት እየሞቱ ነዉ።ጦርነቱ ወትሮም የተዳከመዉን የሐገሪቱን ምጣኔ ሐብት እያሽመደመደዉ ነዉ።

ምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

በዓለም በተለይም በአፍሪቃዉያን ዘንድ የነፃነት አብነት፣ የረጅም ጊዜ የመንግሥትነት ምሳሌ፣የዲፕሎማሲ ማዕከል የነበረችዉን ሐገር በምዕራባዉያን የተገለለች፣ከተባበሩት መንግስታት  ድርጅት ጋር ሳይቀር የዲፕሎማሲ እሰጥ አገባ የገጠመች፣ የብዙ ሚሊዮን ተመፅዋቾች መኖሪያ አድርጓታል።

 

ማዕቀብም ተጥሎባታል።ተፋላሚ ኃይላት ዉጊያ አቁመዉ ካልተደራደሩ ዩናያይትድ ስቴትስና የአዉሮጳ ሕብረት በኢትዮጵያ በመንግስትና በሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሓት) ባለሥልጣናት ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ ለመጣል እየዛቱ፣ ሌሎች መንግስታትንም እያስተባበሩ ነዉ።ተፋላሚዎች ግን እስካሁን ጦርነቱን ለማቆም የፈቀዱ አይመስሉም።ለምን? እና ደግሞስ እስከመቼ? የጦርነቱ ሒደትና የዲፕሎማሲዉ ግፊት የዛሬ ዉይይታችን ትኩረት ነዉ።ሶስት እንግዶች አሉን።

ምስል፦ AP Photo/picture alliance
  1. አቶ ፍፁም አረጋ፣ በዩናይትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር
  2. አቶ ጥሩነሕ ገምታ፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) የፅሕፈት ቤት ኃላፊ
  3. አቶ ባይሳ ዋቅወያ፣ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያና የቀድሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣን ናቸዉ።

 

ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW