1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ

ዓርብ፣ መስከረም 15 2013

የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንዳሉት ኢትዮጵያ የምትገነባዉ ግድብ  የጠብና ዉዝግብ ምክንያት ሊሆን አይገባም።

Dina Mufti Sprecher Außenminister Äthiopien
ምስል Getachew Tedla

የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጫ

This browser does not support the audio element.

 

ኢትዮጵያ በዐባይ ወንዝ ላይ ግዙፍ የኤሌክትሪካ ኃይል ማመንጫ ግድብ  በመገንባቷ ሰበብ የሚወዛገቡት የራስዋ የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ ባለስልጣናት ለመስከረም 4 ይዘዉት የነበረዉን የድርድር ቀጠሮ የሰረዘችዉ ኢትዮጵያ እንዳልሆነች የሐገሪቱ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ።የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እንዳሉት ኢትዮጵያ የምትገነባዉ ግድብ  የጠብና ዉዝግብ ምክንያት ሊሆን አይገባም።ቃል አቀባዩ የድምፃዊ ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያና መዘዙ ያደረሰዉ ጥፋት በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያቀረበዉን ሐሳብ የኢትዮጵያ መንግስት ያልተቀበለበትን ምክንያት፣ ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) አዲስ አበባ የሚገኘዉን ቢሮዉን ወደ ሌላ ለማዞር ሥለ ማቀዱንም ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸዉ ጥያቄ መልስና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ


 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW