ዋስትና የተፈቀደላቸው የኦነግ አባላት እንዳልተፈቱ ጠበቃቸው ተናገሩ
ረቡዕ፣ ጥር 12 2013![Logo Oromo Liberation Front](https://static.dw.com/image/44707714_800.webp)
ማስታወቂያ
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር አባላት የሆኑ ፖለቲከኞች ድምፃዊ ሐጫሉ ሁንዴሳ ከተገደለ በኋላ በተቀሰቀሰ ኹከት ተጠርጥረው ከታሠሩ በኋላ ፍርድ ቤት ዋስትና ቢፈቅድላቸውም እስከዛሬ አልተፈቱም። ከእነዚህ መካከል ለሚ ቤኛ፣ ዳዊት አብደታ እና ኮሎኔል ገመቹ አያና ይገኙበታል። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወል ሱልጣን ግን በዋስትና የተፈታ ሰው ተጠርጣሪ የዋስትና ጊዜውን ጠብቆ ወደ ፍርድ ቤት ሳይቀርብ ቀርቶ ትዕዛዝ ከተሰጠ ብቻ ነው።
ስዩም ጌቱ
ሸዋዬ ለገሠ