1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ውይይት፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ዝግጅት

ሰኞ፣ የካቲት 11 2011

ተፎካካሪዎች፣ አስመራጭና ተመራጮች በዚሕ አጭር ጊዜ ዉስጥ ተወያይተዉ፣ ተስማምተዉ፣ አወዳድረዉ፤ ወይም ተወዳድረዉ፣ ሐገር አረጋግተዉ፣ ሕዝብ ቆጥረዉ ነፃና ትክክለኛ ምርጫ ማድረግና መምራት መቻላቸዉ እያጠያየቀ ነዉ

Äthiopien Wahlen 2015
ምስል DW/E. Bekele

ውይይት፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ዝግጅት

This browser does not support the audio element.

እስካሁን በተያዘዉ ዕቅድ መሠረት ኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ የምታስተናግድበት ጊዜ ከዓመት በላይ ብዙም አልቀረዉም።የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮችና የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለሥልጣናት ግን የቦርዱን ኃላፊነት፣ አሠራር፣ አወቃቀር፣ደንብንና ምናልባትም መሪዎቹን ለማሻሻልና ለመቀየር ገና እየተወያዩ ነዉ።የብዙ አካባቢ ፀጥታም አስተማማኝ አይደለም።በዚያ ላይ የኢትዮጵያ ማዕከላዊ የስታትስቲክስ መስሪያ ቤት የሐገሪቱን ሕዝብ ለመቁጠር ገና እየተዘጋጀ ነዉ።በዚሕም ምክንያት የመራጩን ሕዝብ ትክክለኛ ቁጥር በዉል መናገር አይቻልም።እስካሁን ባለን መረጃ ግን ከ36 እስከ 40 ሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ  ድምፅ ይሰጣል ተብሎ ይገመታል።ተፎካካሪዎች፣ አስመራጭና ተመራጮች በዚሕ አጭር ጊዜ ዉስጥ ተወያይተዉ፣ ተስማምተዉ፣ አወዳድረዉ፤ ወይም ተወዳድረዉ፣ ሐገር አረጋግተዉ፣ ሕዝብ ቆጥረዉ ነፃና ትክክለኛ ምርጫ ማድረግና መምራት መቻላቸዉ እያጠያየቀ ነዉ።አጠያያቂዉ ጉዳይ የዉይይታችን ትኩረት ነዉ።ሰወስት እንግዶች አሉን።

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW