1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ውጤት ያላስገኘው የደቡብ ሱዳን ውይይት

ሐሙስ፣ ግንቦት 16 2010

በጎርጎሪዮሳዊው 2015 ዓም የከሸፈውን የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት እንደገና ለማነቃቃት በአዲስ አበባ ስብሰባ ትናንት ሌሊት ካላንዳች ስምምነት ተጠናቀቀ። ለአስር ቀናት የዘለቀው ስብሰባው በዋነኛነት በደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ወገኖች መካከል የሚታየውን ልዩነት የማጥበብ ዓላማ ይዞ የተነሳ ነበር።

Troika bei den Verhandlungen für Südsudan in Addis Abeba
ምስል DW/G. Tedla

መፍትሔ ያልተገኘለት የደቡብ ሱዳን ውዝግብ

This browser does not support the audio element.

የአደራዳሪነቱን ሚና የያዘው የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት እንደገለጸው፣ ተቀናቃኞቹ ወገኖች በስልጣን መጋራቱ እና በፀጥታ ጥበቃ ጉዳዮች ላይ አስማሚ ሀሳብ ላይ በመድረስ የርስ በርሱን ጦርነት እንዲያበቁ ቀናት በተጠናከረ ሁኔታ ያደረገው ጥረት ፍሬ ሳያስገኝ ቀርቷል። በድርድሩ የተገኙት የኖርዌይ፣ የዩኤስ አሜሪካ እና የብሪታንያ ተወካዮች ኢጋድ ተቀናቃኖቹን ወገኖች ለማግባባት የጀመረውን ጥረት እንዲገፋበት ጠይቀዋል። በርስበርሱ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ ሱዳናውያን የተገደሉ ሲሆን፣ ሚልዮኖችም ተፈናቅለዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ 

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW