1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዓለም አቀፍ የዕውቀት ልውውጥ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 1 2005

ረሃብን ለመቅረፍ በሽታን ለመከላከል፣ መሠረተ ልማትን በሰፊው ለመዘርጋት ፣ በአጠቃላይ ኑሮን ለማሻሻል፤ ዕውቀት ወሳኝ ነው። ዕውቀት የሚስፋፋው ፤ የሚዳብረው ፣ በመመራመርና ከሌሎች ጋር የሐሳብ ልውጥ በማድረግ ነው። ይህን በማከናወን ቀዳሚውን ቦታ

ምስል NASA

የሚይዙት : በየዘርፉ የተሠማሩ ተማራማሪ ምሁራን ናቸው። በእንዲህ ሁኔታ የሚስፋፋውን ዕውቀት፣ በተመክሮ ከዳበረ ዕውቀትና ልምድ ጋር አጣምሮ መጠቀሙ ፣ ለታዳጊ ሀገራት በተለይ ፣ አብነቱ የሚያጠያይቅ አይደለም።

ምስል SNAP GmbH

ጥቂት ኢትዮጵያውያን ምሁራን ፣ በብሪታንያ መዲና ፣ በለንደን ፣ የጀመሩት ተሰባስቦ የመምከር፤ ሐሳብ የመለዋወጥ ተመክሮ ፣ ሰፊ ጠቀሜታ እንዳለው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሥመሰከረ ሳይመጣ አልቀረም።

ዘመኑ ባስገኘው የኢንተርኔት መገናኛ ስልት የሚመክሩ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ፣ በዚሁ የግንኙነት መረብ ብቻ ሳይሆን በአካልም ፤ ከዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ወዳጅ ምሁራን ጋር እየተገናኙ የሚመክሩበት መድረክ ዘንድሮም ሆነ በመጪው ዓመት በኅዳር ወር 2ኛ ሳምንት ገደማ ላይ 3ዓመት ይሆነዋል።

ለመጪው ጉባዔ፣ ተመራማሪዎች በአጠቃላይ ምሁራን ጠቃሚ ጽሑፎቻቸውን እስከ ነሐሴ 9 ,2005 (እ ጎ አ እስከ ነሐሴ 15 ,2013)እንዲያቀርቡ ተጠይቀዋል። የዚህ ዓይነቱ ጉባዔ ፣ ለሀገር ዕድገት ካለው አስተዋጽዖ አኳያ፣ የጉባዔውን ዋና አስተባባሪና ሊቀመንበር ፤ የ London South Bank University ባልደረባ የሆኑትን ዶክተር አማረ ደስታን ለቀጣዩ ጉባዔ የምርምር ውጤቶች እንዲቀርቡ ለተላላፈው ጥሪ እስካሁን ምን ዓይነት ምላሽ እንደተገኘ ያብራሩልን ዘንድ ጠይቄአቸው ነበር---------

(ድምፅ)

ተክሌ የኋላ

ሸዋዬ ለገሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW