1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ኪነ ጥበብኢትዮጵያ

ሠዓሊዋ አቢጌል እሸቱ

04:51

This browser does not support the video element.

ዓርብ፣ ኅዳር 14 2016

“ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት እቤት መዋል ስጀምር ውስጤ የነበረውን የሥዕል ፍላጎት ይበልጥ እንዳዳብር መልካም አጋጣሚ ሆኖልኛል” ትላለች የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ተማሪ አቢጌል እሸቱ ፡፡ አቢጌል አሁን ላይ የ18 ዓመት ወጣትና የ11ኛ ክፍል ተማሪ መሆኗን ትናገራለች፡፡

በኦን ላይን በወሰደችው የሥዕል ሥልጠና ከሥሜት መግለጫነት ባለፈ የገቢ ምንጭ እንደሆናት የጠቀሰችው አቢጌል በአሁኑ ወቅትም ለተለያዩ ቤተሰቦችና ድርጅቶች ሥዕሎችን በክፍያ እንደምትስል ገልጻለች፡፡  በኢትዮጵያ የሥዕል ጥበብ ብዙም ትኩረት ያልተሰጠው የኪነ ጥበብ ዘርፍ መሆኑን የምትናገረው አቢጌል “ አሁን ላይ የሥዕል ሥሜት ከእኔ አልፎ ቤተሰቦቼም አንዲጋሩት አድርጊያለሁ ፡፡  በቀጣይ በዚህ ሙያ የራሴን አሻራ ለማሳረፍ እቅድ አለኝ ፡፡ ሌሎች ወጣቶች ለራሳቸው ጊዜ በመስጠት እንደየዝንባሊያቸው ጥረት ማድረግ አለባቸው “ ብላለች ፡፡
 #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute

ዘገባ: ሊሻን ዳኜ
ቪድዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ   

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW