1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: ሴት ስኬተሮች

05:17

This browser does not support the video element.

ሰኞ፣ ነሐሴ 23 2014

ስኬት ቦርድ መንዳት ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙም የተለመደ አይደለም። በተለይ ደግሞ ሴት ኢትዮጵያውያን ሲነዱ አይስተዋልም። ይሁንና ከቅርብ ዓመታት አንስቶ ቢያንስ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ይህንን የሚነዱ ወጣቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱ መጥተዋል።

በአዲስ አበባ መካኒሳ አካባቢ በቡድን ተሰባስበው ስኬት ቦርድን የሚለማመዱ ሴት ታዳጊዎች ለዶይቼ ቬለ ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች ዘጋቢ ሱመያ ሳሙኤል እንደገለፁላት ስፖርቱ ደፋር አድርጓቸዋል፣ በራስ መተማመናቸውም ጨምሯል። የሴት ስኬትቦርዲንግ መስራች ህሊና ሰለሞን «ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት 13 ሴት አባላት እና 10 ስኬት ቦርዶች አሉት» ትላለች። ሴቶቹ ስኬት ቦርድ የሚነዱት ለጊዜ ማሳለፊያ ወይም እዛ ላይ ሆኖ ፎቶ ለመነሳት ሳይሆን ወደፊት ስፖርቱን ሙያቸው አድርገው ሀገራቸውን ማስጠራት ስለሚፈልጉም እንደሆነ ነግረውናል። #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute

ዘገባ፡ ሱመያ ሳሙኤል
ቪዲዮ፡ ሥዩም ጌቱ (DW) ከአዲስ አበባ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW