ስፖርትአፍሪቃዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: ባለቴኳንዶዎቹ እንስቶች 04:57This browser does not support the video element.ስፖርትአፍሪቃ1 ሰኔ 2013ማክሰኞ፣ ሰኔ 1 2013ከፍተኛ አካላዊ አንቅስቃሴ በሚጠይቀው የቴኳንዶ ስፓርት ኢትዮጵያ ውስጥ ሴቶች ሲሳተፉ ማየት ብዙም የተለመደ ላይሆን ይችላል ። በርካቶች "ትሰባበራላችሁ፣ ይቅርባችሁ" ይሉን ነበር የሚሉት መቅደስ እዮብ እና በረከት በቀለ ወደ ስፖርቱ ከገቡ በኋላ ቴኳንዶን ከጠበቁት በላይ አስደሳች ሆኖ እንዳገኙት ይናገራሉ። ማገናኛዉን ኮፒ አድርግማስታወቂያመቅደስ በቴኳንዶ አራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ሰማያዊ ቀበቶ አላት። በረከት ደግሞ ገና ጀማሪ ናት። የወደፊት ህልሟ ጥቁር ቀበቶ መያዝ ነው። የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች ዘጋቢ ሊሻን ዳኜ ታዳጊዎቹ ወደሚሰለጥኑበት በሐዋሳ ከተማ የሚገኘው የወጣቶች ማዕከል በመሄድ አነጋግራቸዋለች። ዘገባ: ሊሻን ዳኜ ቪዲዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ