1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች

03:56

This browser does not support the video element.

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 26 2014

በሀዋሳ ከተማ ሰሞኑን በተካሄደው አገር አቀፍ የዌልቸር (የተሽከርካሪ ወንበር) ቅርጫት ኳስ ውድድር ከተሳተፉት ወጣት አካል ጉዳተኞች መካከል የ19 ዓመቷ ሠዓዳ አብደላ አንዷ ናት።

የደቡብ ክልል የቅርጫት ኳስ ቡድንን በመወከል ከጉራጌ ዞን ወልቂጤ የመጣችው ሠዓዳ በውድድሩ ያሳየችው እንቅስቃሴ የብዙዎችን ትኩረት እንድታገኝ አድርጓታል፡፡ አብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል አካል ጉዳተኞች በስፖርት ዘርፍ ይሳተፋሉ የሚል ግምት እንደሌለው የምትናገረው ሠዓዳ « ስፖርቱ ለእኔ ብዙም አልከበደኝም» ትላለች ፡፡ በቴክኒክ ሙያ ተመርቃ ስራ ያላገኘችው ሠዓዳ በአሁኑ ሰዓት ትኩረቷን ስፖርቱ ላይ አድርጋለች።

ዘጋቢ ፡ ሊሻን ዳኜ
ቪዲዮ ፡ ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW