1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከጎዳና እና ሱስ የተላቀቀችው ሐና

04:49

This browser does not support the video element.

ረቡዕ፣ መስከረም 4 2015

በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆነችው የ18 ዓመቷ ታዳጊ ወጣት ሐና ታደለ ላለፉት ሦስት ዓመታት ኑሯዋን በጎዳና አድርጋ መቆየቷን ትናገራለች ፡፡ ‹‹ የጎዳና ሕይወት በተለይ ለሴቶች በጣም አስቸጋሪ ነው ›› የምትለው ሐና ቦታው ጾታዊ ጥቃትን ጨምሮ ለተለያዩ ሱሶች እንደሚያጋልጥ ካሳለፈችው ህይወት በመነሳት ትገልጻለች ፡፡ 

በአንድ የበጎ አድራጎት ድርጅት አማካኝነት ባገኘችው የሥነ ልቦና ድጋፍ አሁን ላይ ከተለያዩ ሱሶች መላቀቋን የምትናገረው ሐና ‹‹ ቀጣይ ሕይወቴን የተሳካ ለማድረግም በባጃች ታክሲ አሽከርካሪነት ሙያ እየሠለጠንኩ እገኛለሁ ›› ብላለች ፡፡ ሐናን ጨምሮ ኑሯቸውን በጎዳና ያደረጉ አዳጊ ወጣቶችን እየደገፈ የሚገኘው እና «ሴንተር ኦፍ ኮንሰርን» በተባለው በጎ አድራጎት ድርጅት ውስጥ በሥነ ልቦና ባለሙያነት እያገለገሉ የሚገኙት ተስፉ ዋርጃ በበኩላቸው በጎዳና ላይ የሚገኙ አዳጊዎችና ወጣቶች ከአካላዊ ጉዳት እስከ ሞት የሚደርሱ ጥቃቶች እየተፈጸሙባቸው ይገኛሉ ይላሉ፡፡ #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute


ዘገባ ፦ ሊሻን ዳኜ
ቪዲዮ ፦ ሸዋንግዛው ወጋየሁ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW