1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ኪነ ጥበብኢትዮጵያ

የሥዕል አፍቃሪዋ አይነ ስውር

04:31

This browser does not support the video element.

ረቡዕ፣ ኅዳር 12 2016

ሲሃም ጀማል ብርቱ እና መሞከር የማትወድ ሴት ባትሆን ኖሮ አሁን በኩራት ተምትናገረውን "ሥዕልን የማየት" ልዩ ፍላጎትን፣ በሥዕልም ይሁን በሙዚቃ እና ሌሎች የኪነ ጥበብ ሥራዎች ላይ ትንታኔ መስጠት የምትችልበትን የራዲዮ ዝግጅት ማሰናዳት ባልቻለች ነበር። የሀሳብ ገበታ የሚል የራዲዮ ዝግጅት አላት።

ሲሃም ጀማል ገና የሁለት ዓመት ልጅ እያለች በደረሰባት የጉሮሮ ወይም ቶንሲል ህመም ምክንያት የውድ ዐይኖቿን ብርሃን ተነጥቃ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ዐይነስውር ሆናለች። 
ሲሃም የመጀመርያ ደረጃ ትምህርቷን የተማረችበት አዲስ አበባ የሚገኘው የጀርመን ስኩል ትምህርት ቤት ለዛሬ ማንነቷ በጎ አሻራ አሳርፎላታል። 
ዐይነስውር መሆን ብሎም ሴት እና ወጣት መሆን የሚፈጥሩትን ጫና እየተቋቋመች ሕይወትን የምትመራው ሲሃም በተማረችበት የሕግ ሙያም ልዩ ልዩ ሥራዎችን ትሠራለች ። በዚሁ ምክንያት ወደ ተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጓዝ እድልም አግኝታለች። 
ከሲሃም ጋር ስለ ዝንባሌዎቿ ፣ ዐይነስውርነትን ተቋቁማ ሕልሞቿን ለማሳካት ስለምታደርገው ጥረት፣ ፈተናን እንዴት ማለፍ እንደሚቻልና ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጋር እንዴት ራሷን አስማምታና ተምራ እንደምትኖር አጭር ቃለ መጠይቅ አድርገንላታል።  #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute  


ዘገባ: ሱመያ ሳሙኤል
ቪዲዮ: ሰለሞን ሙጬ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW