የሰላም ባህል እና መቻቻል ውይይት
ዓርብ፣ ኅዳር 10 2014![Äthiopien | GirlzOffMute](https://static.dw.com/image/59729691_800.webp)
ማስታወቂያ
መቅደስ እና ቤተልሔም በሰላም ክበብ ውስጥ በመሳተፍ የሰላም እና መቻቻል ባህል እንዲዳብር ይሰራሩ። «ሰላም መጀመሪያ ከቤት ውስጥ ነው የሚጀምረው የምትለው» ቤተልሔም ከህፃንነቷ አንስቶ ሰላም ማስከበር ደስ እንደሚላት ትናገራለች። የክበብ አባልም የሆነችው በዚህ ምክንያት ነው። ወጣቶች በክበብ ውስጥ ያገኙትን እውቀት ሚኒ ሚዲያ ላይ እና ክፍላቸው ውስጥ ያሉ ተማሪዎችን በማካፈል ሀሳብ እንደሚለዋወጡ ይናገራሉ። መቅደስ « እኔ ለምሳሌ የክፍል አለቃ ነኝ፤ ክፍት ክፍለ ጊዜ ካለ በስብሰባ ላይ ያገኘሁትን እውቀት ማስታወሻዬን በማውጣት በዛ አማካኝነት ለሌሎች አካፍላቸዋለሁ ትላለች።» ወጣቶቹን ያወያየችው በሀዋሳ የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች ዘጋቢ ሊሻን ዳኜ ናት ።
ሊሻን ዳኜ
ሸዋንግዛው ወጋየሁ