1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: የሴት ልጅ ግርዛት ትግል

03:54

This browser does not support the video element.

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 5 2013

ኢትዮጵያ ውስጥ አሁንም ድረስ የሴት ልጅ ግርዛት በድብቅ ይፈፀማል። በድሬደዋ ከተማ በሚገኝ አንድ ማዕከል የሴቶችና ህፃናት ጥቃት የወንጀል ምርመራ ማስተባበርያ ኃላፊ የሆኑት ምክትል ኢንስፔክተር ጥላሁን ቸርነት ለዝግጅታችን እንደገለፁት በቅርቡ ወላጆቿ አስገርዘዋት እና ለሳምንት ያህል ቤት ውስጥ አቆይተዋት ልጅቷ ክፉኛ በመታመሟ የተነሳ ወደ ሀኪም ቤት ስለወሰዷት ድርጊቱ ሊጋለጥ ችሏል።

በድሬደዋ ከተማ በሚገኝ አንድ የህፃናት መብት ጥበቃ ክበብ አባል የሆኑት ዮሐንስ ሀብታሙ እና ቅድስት አያሌው ለምሳሌ ይህንን ጎጂ ልማድ ለማስቆም የምክር አገልግሎት በመስጠት የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ። የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች ዘጋቢ ሊዲያ መለስ ድርጊቱ የተፈፀመባቸው ሴቶችን በአካል አግኝታ ለማነጋገር ባትችልም የሴት ልጅ ግርዛት ስለሚያስከትለው ጉዳት የሴቶች፣ ወጣቶች እና የኤች አይ ቪ ባለሙያም አነጋግራ በዛሬው የዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች ዝግጅት ትጠብቃችኋለች።
ዘገባ: ሊዲያ መለስ
ቪዲዮ: መሳይ ተክሉ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW