1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: ባለብዙ ተሰጥኦዋ ታዳጊ

03:57

This browser does not support the video element.

ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ሰኞ፣ መስከረም 19 2018

ግጥም እና ድርሰቶችን ትጽፋለች ፣ ክራርና በገናን ደግሞ አሳምራ ትጫወታለች፡፡ የ14 ዓመቷ ታዳጊ ማስተዋል መዝገቡ ፡፡ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ የሆነችው ታዳጊ ማስተዋል የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ናት ፡፡ ዐይነ ሥውርነቷ የውስጥ ጥበባዊ ፍላጎቷን ከማውጣት አላገዳትም ፡፡ በአንድ ጊዜ የተለያዩ ተሰጥኦዎች ባለቤት የሆነችው ማስተዋል ወደ ጥበቡ የመጣችው ከልጅነቷ ጀምሮ ባዳበረችው የግጥም ጹሁፍ እና የሙዚቃ መሣሪያ ልምምድ መሆኑን ገልጻለች ፡፡

ማስተዋል ከግጥም እና ከዝማሬ ሥራዎቿ በተጨማሪ “ ምክሬን ላካፍላችሁ “ በሚል ርዕስ ለዕድሜ አኩዮቿ የሚውል መጸሀፍ ለህትመት አብቅታለች ፡፡ መጽሀፉ በውስጡ መንፈሳዊና ሥነ ልቦናዊ ይዘቶችን የያዘ ነው ብላለች ፡፡
አሁን ላይ የታዳጊ ማስተዋል ዝማሬዎች በተለያዩ የ ዩ ቲዩብ ቻናሎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እየተመለከቷቸው ይገኛሉ ፡፡ ግጥሞቿን ፣ ድርሰቶቿን እና ዝማሬዎቿን አስመልክቶ ሰዎች በጎ አስተያየቶችን በመስጠት እንደሚያበረታቷት ጠቅሳለች ፡፡
ለአካል ጉዳተኛ መብቶች ለሚሟገቱ የህግ ባለሙያዎች የተለየ አድናቆት እንዳላት ገልጻለች ፡፡አሷም ወደፊት የህግ ባለሙያ የመሆን ፍላጎት እንዳላትና ለዚህም እንደምትጥር ተናግራለች ፡፡ በአካል ጉዳት ውስጥ ለሚገኙ ታናናሾቼ እና ታላላቆቼ መልዕክት አለኝ የምትለው ታዳጊዋ “ ዐይነ ስውራንም ሆንን ሌሎች አካል ጉዳተኞች የማይቻል ምንም ነገር እንደሌለ ማመን አለብን ፡፡ ትልቅ ቦታ ደረሰን ማህበረሰባችንን እና አገራችንን መጥቀም እንችላለን “ ብላለች ፡፡  #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute

ዘገባ: ትንቢት ሰውነት
ቪድዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ  
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW